عربيEnglish

The Noble Qur'an Encyclopedia

Towards providing reliable exegeses and translations of the meanings of the Noble Qur'an in the world languages

Competition [At-Takathur] - Amharic translation - Africa Academy

Surah Competition [At-Takathur] Ayah 8 Location Maccah Number 102

1. (በዚህች ዓለም ጸጋዎች) ብዛት መፎካከር (ጌታችሁን ከመገዛት) አዘናጋችሁ::

2. መቃብሮችን እስከጎበኛችሁ ድረስ:: (በዚሁ ላይ ቀጠላችሁ)።

3. ከዚህ ተግባራችሁ ተከልከሉ (ታቀቡ):: ወደፊት (ውጤቱን) ታውቃላችሁ፤

4. ከዚያም ከዚህ ተግባራችሁ ተከልከሉ። ወደ ፊትም ታውቃላችሁ፤

5. በእውነቱ (የሚጠብቃችሁን) በእርግጠኝነት ብታውቁ ኖሮ (ይህን ያክል ባልተዘናጋችሁ ነበር)።

6. ገሀነምን በእርግጥ ታያላችሁ::

7. ከዚያም እርግጠኛን ማየት ታዩዋታላችሁ፤

8. ከዚያም በድሎታችሁ ጉዳይ ሁሉ በዚያ ቀን ትጠየቃለችሁ::