عربيEnglish

The Noble Qur'an Encyclopedia

Towards providing reliable exegeses and translations of the meanings of the Noble Qur'an in the world languages

The morning star [At-Tariq] - Amharic translation - Africa Academy

Surah The morning star [At-Tariq] Ayah 17 Location Maccah Number 86

1. በሰማዩ እና ሌሊት በሚመጣውም እምላለሁ።

2. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የሌሊት መጪው ምን እንደሆነ ምን አሳወቀህ?

3. ጨለማውን ሰንጣቂ ኮከብ ነው::

4. ነፍስ ሁሉ በእርሷ ላይ ጠባቂ ያለባት እንጂ ሌላ አይደለችም::

5. የሰው ልጅ ከምን እንደተፈጠረ ይመልከት፤

6. ከተስፈንጣሪ ውሃ (የዘር ፈሳሽ) ተፈጠረ::

7. ከጀርባና ከእርግብግቢቶች መካከል የሚወጣ ከሆነ የዘር ፈሳሽ ውሃ (ተፈጠረ)።

8. አላህ እርሱን በመመለሱ ላይ በእርግጥ ቻይ ነው::

9. ሚስጥሮች በሚገለጹበት ቀን፤

10. (ለሰው) ምንም ኃይልና ረዳት አይኖረዉም::

11. የመመለስ ባለቤት (ዝናባማ) በሆነችው ሰማይ እምላለሁ::

12. (በበቃይ) የመሰንጠቅ ባለቤት በሆነችው ምድርም እምላለሁ::

13. እርሱ (ቁርኣን)፤ (እውነትን ከውሸት) የሚለይ (የአላህ) ቃል ነው።

14. እርሱም ቀልድ አይደለም።

15. እነርሱ በእርግጥ ተንኮልን ያሴራሉ (ይሸርባሉ)::

16. እኔ ተንኮልንም እመልሳለሁ (አመክናለሁ)::

17. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ከሓዲያንን ቀን ሰጣቸው:: ጥቂትን ጊዜ አቆያቸው (ታገሳቸው)::