عربيEnglish

The Noble Qur'an Encyclopedia

Towards providing reliable exegeses and translations of the meanings of the Noble Qur'an in the world languages

The earthquake [Al-Zalzala] - Amharic translation - Africa Academy

Surah The earthquake [Al-Zalzala] Ayah 8 Location Madanah Number 99

1. (መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ምድር በኃይል መንቀጥቀጧን በተንቀጠቀች ጊዜ፤

2. ምድርም ሸክሞቿን ባወጣች ጊዜ፤

3. ሰዉም "ምን ሆነች?" ባለ ጊዜ፤

4. በዚያ ቀን ወሬዎቿን ትናገራለች::

5. ጌታህ ለእርሷ አሳውቋታልና፤

6. በዚያ ቀን ሰዎች ሁሉ ስራዎቻቸውን እንዲያዩ ይደረጉ ዘንድ እንደየስራቸው የተበታተኑ ሆነው ከየመቃብራቸው ወደ መቆሚያው ስፍራ ይመለሳሉ::

7. የብናኝን ክብደት ያህል መልካም የሰራ ሰው ያገኘዋል::

8. የብናኝን ክብደት ያህል ክፋት የሰራ ሰውም ያገኘዋል::